የሜልበርን ኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላት ኦቦ አብደታ ሆማ፣ ኦቦ ዳኜ ደፈርሻ፣ ኦቦ በንቲ ኦሊቃ እና አዴ ኢፍቱ ሚደቅሳ በተለይ በተከታታይ ለዓመታት ለኢሬቻ በዓል ትውውቅና አከባበር ላበረከቱት የማኅበረሰብ አገልግሎቶች የዘንድሮውን የብሩስ በጎ ፈቃደኞች ዕውቅና ሽልማት ከፌዴራል ኢሚግሬሽንና ዜግነት ረዳት ሚኒስትር ጁሊያን ሂል እጅ ተቀብለዋል።